Set Political Prisoners Free !
Your Ad Here

ከዚህ በሁዋላ ከጳውሎስ ጋር አብረን አንሠራም

ከዚህ በሁዋላ ከጳውሎስ ጋር አብረን አንሠራም

ደጀ ሰላም:Paulos on uniform
• “ከዚህ በሁዋላ ከከጳውሎስ ጋር አብረን አንሠራም” ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ፤ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ
• “ሀገረ ስብከቴን ተረከቡኝ” ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣
• ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ ያልተጠበቁ የፓትርያርኩ ደጋፊ፣
• ፓትርያርኩ “ተቃዋሚዎቻቸውን ይበቀላሉ” ይባላል፣
• አቡነ ሳሙኤልን ስላገቱት ሰዎች ፌዴራል ፖሊስም አያውቅም፣

ቅዱስ ሲኖዶሱ ያረቀቀውን ቃለ ጉባዔ ሳያጸድቅ፣ የጀመረውን አጀንዳ ሰይቋጭ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን ሜዳ ላይ ጥሎ ወደ ቤቱ ገብቷል። ከስምምነት ላይ የተደረሰበት ውሳኔ በፊርማ እንዳይጸድቅ ብፁዓን አበው እስጢፋኖስ፣ ኤጲፋንዮስና ጎርጎርዮስ የሞት ሽረት ትግል አድርገው፣ አባቶችን በጥብጠው ውሳኔው እንዲከሽፍ አድርገዋል። በተለይም በምዕራብ ኢትዮጵያ በጀመሩት መልካም አገልግሎት በሕዝቡ እየተመሰገኑ የነበሩት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ይህንን ገዳይ አቋም እንዴት ሊይዙ እንደበቁ እንቆቅልሽ ሆኗል። ገሚሱ በገንዘብ ተገዝተው ነው ሲል ሌላው ደግሞ ውስጠ ዘ በሆነ ማስፈራሪያ ሊሆን ይችላል እያለ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደ አሸናፊነቱ እየመጡ ያሉት ፓትርያርኩ የበቀል በትራቸውን እንደሚመዙ እየተጠበቀ ነው። የመጀመሪያ ተጠቂዎች የሚሆኑት በአዲስ አበባ የሚገኙ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ሲሆኑ ባለፈው ሳምንት በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል መሪነት ስብሰባ ካደረጉ በሁዋላ የፓትርያርኩን ድርጊት የሚቃወም መግለጫ ማውጣታቸው ይታወሳል። ከዚህም ባሻገር ይህንን ሁሉ ሕዝብ ያስተባብርብኛል ያሉት ማህበረ ቅዱሳንም ላይ ጥርሳቸውን ነክሰዋል ተብሏል።

የቤተ ክህነቱ ድራማ ዛሬ ሲተወን ጠዋት በማለዳው ስብሰባ እንዳይገቡ የታገቱት ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ለምን እንደታገቱ ፌዴራል ፖሊስ ራሱ አያውቅም። የደህንነት ክፍሉ ደግሞ ለደህንነታቸው ብዬ ነው ብሏል። ድራማው ሊቀ ጳጳሱን ከስብሰባው በማስቀረት ውሳኔውን ማክሸፍ ከሆነ በርግጥም ዘዴው ሰርቷል ማለት ይቻላል።መንግሥት በበኩሉ ጉዳዩን እያጠናው እንደሆነ ውስጥ አዋቂዎች ገልጸዋል።

በተያያዘ ዜና ፓትርያርኩ የተነሣባቸውን ተቃውሞ ለመስበርና አባቶችን አንገት ለማስደፋት የሚሆን ገንዘብ ራሳቸው በግላቸው ከሚያዙበት ከቁልቢ ገብርኤል ካዝና ወጪ መደረጉ ታውቋል። የብሩ መጠን ለጊዜው ባይታወቅም ገንዘቡ ለአንዳንድ የፖሊስ ሃላፊዎች፣ ደህንነቶችና ጉልበት ላላቸው ሰዎች መበተኑ ሲታወቅ መንግሥት በውስጡ ሌላ መንግሥት ያለበት አስመስሎታል። እስከ ዛሬም በመንግሥት ስም ቤተ ክርስቲያኒቱን እግርተወርች አስረው ሲበሏት፣ ሲግጧትና ሲያዋርዷት የነበሩ ሰዎች የፓትርያርኩ ዘመዶችና ወዳጆች ብቻ ሳይሆኑ በመንግሥት ሥልጣን ላይ የተንፈራጠጡ ሰዎችም መሆናቸው እየተገለጸ መጥቷል። መንግሥት ጉዳዩን አጣርቶ ሕገ ወጦቹ እጃቸውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ እንዲያነሱ ያደርጋል ተብሎ ይገመታል።

ነገሩ በዚህ ከቀጠለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ አላት ለማለት እንደማያስደፍር አንድ ሊቀ ጳጳስ ተናግረዋል። ከዋሺንግተን ዲሲ ተጠርተው የተሾሙት የሲዳሞ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሥራ አስፈጻሚው አባል ብፁዕ አቡነ ፋኑኤልም በበኩላቸው “ሀ/ስብከቴን ተረከቡኝ” ማለታቸው ተሰምቷል። በርግጥም ሊቀ ጳጳሱ እንዲህ ካደረጉ ጳጳሳት የሥራ መልቀቂያ የሚያስገቡበት፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ሳይሆን በፓትርያርክና በሴት ወይዘሮዎች ብቻ የሚመራ ቤተ ክህነት ይፈጠራል ማለት ነው።

አንድ አስተያየት ሰጪ እንደተናገሩት የፊታችን ሰኞ ስብሰባ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ስብሰባው የተጠራው በቅዱስ ፓትርያርኩ ከመሆኑ አንጻር ምንም ተለየ ነገር አይጠበቅም። ቅዱስነታቸው የፊታችን እሑድ በዓለ ሲመታቸውን እንደሚያከብሩ ይታወቃል።

 

We recommend to you to visit the following sites:

     

EthioSun

This website uses IntenseDebate comments, but they are not currently loaded because either your browser doesn't support JavaScript, or they didn't load fast enough.

Leave a Comment

We welcome your comments if they are civil. All spam, profane, abusive and off topic comments will never be posted. Repeat offenders will be blocked. The detail explanation of rules of conduct can be found in our Terms of Service. ethiosun.com




No results.

Who's Online

  • 0 Members.
  • 13 Guests.

Amharic

በዋሽንግተን ዲሲ ለአርቲስት ታማኝ በየነ ታላቅ የክብር ምሽት ተደረገበዋሽንግተን ዲሲ ለአርቲስት ታማኝ በየነ ታላቅ የክብር ምሽት ተደረገ

በዋሽንግተን ዲሲ ለአርቲስት ታማኝ በየነ ታላ...

ኑሮ ያሇ ነጻነት ግማሽ ሞትኑሮ ያሇ ነጻነት ግማሽ ሞት

By Geletaw Zeleke: የሰዉ ሌጅ መሰረታዊ ፍሊጎቶቾነው...

የኢሣት ነበልባል በሁሉ ሥፍራ ይንደድ!!የኢሣት ነበልባል በሁሉ ሥፍራ ይንደድ!!

 የኢሣት ነበልባል በሁሉ ሥፍራ ይንደድ!! እኛ ...

የዜግነቴን ላድርስየዜግነቴን ላድርስ

ትውልዶች የየራሳቸውን አስተዳደራዊ ዘዪ እያ...

Read more about the sham election

Tyrants Daughter Got Wild

Get the Flash Player to see the slideshow.