ታላቁ ሩጫ ዘንድሮም በተቃውሞ ድምጽ:-መሰናበቻ መሰናበቻ የቀረችን ብርቱካን ብቻ ፍቱልን እሷን ብቻ!
አውራምባ ታይምስ (አዲስ አበባ)፡-
በ1994 ዓ.ም. የተጀመ ረው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለ9ኛ ጊዜ በዛሬው እለት ተካሄደ፡፡ ውድድሩን እንግሊዛዊቷ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ከደራርቱ ቱሉ እና ከኃይሌ ገ/ሥ ላሴ ጋር በመ ሆን አስጀምራለች፡፡ በታላቁ ሩጫ የተቃውሞ ድምጾች መ ሰማት የጀመ ሩት በ1998 ዓ.ም ህዳር ወር የቅንጅት አመ ራሮችና ጋዜጠኞች መ ታሰራቸውን በመ ቃወም ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየአመ ቱ ወቅታዊ የተቃውሞ ድምጾችን እያስተናገደ እዚህ ደርሷል፡፡
ዘንድሮም ውድድሩ በተካሄደባቸው ጐዳናዎች ላይ “እንነጋገር የብርቱዬን ነገር”፣ “መ ሰናበቻ መ ሰናበቻ የቀረች ዘንድሮም የቀረችን ብርቱካን ብቻ”፣ “እንነጋገር የቤንዚኑን ነገር”፣ “ልብ የሌለው ኃይሉ ሻውል ብቻ ነው”፣ የአለም ጅሉ የኢትዮጵያው ኃይሉ እና መ ሰል ተቃውሟዊ ኃሳቦች የተንሸራሸሩ ሲሆን ካለፉት ዓመ ታት አንፃር ሲታይ ግን የበረከቱ የተቃውሞ
መ ልዕክቶች እና ተሳታፊዎች አልነበሩም፡፡
መ ከላከያ ሚኒስቴር፣ ፍርድ ቤት፣ ቤተ-መ ንግስት፣ ፍትህ ሚኒስቴር አካባቢ የደረሱ ሯጮ ች (ተሳታፊዎች) በኢህአዴግ መ ንግስት ላይ ከፍተኛ የጩ ኸት እና የተቃውሞ ድምጾች ያሰሙ ነበር፡፡ ባለፈው ዓመ ትም ቴዲ አፍሮ እንዲፈታ ለመ ጠየቅ ‹ኦባማ ይፈታ› የሚል ተቃውሞ መ ቅረቡ አይዘነጋም፡፡ በዛሬው የታላቁ ሩጫ ውድድር በሴቶች ኮረኒ ጀሊላ፣ በወንዶች ጥላሁን ረጋሳ የውድድሩን ሪከርድ በመ ስበር ጭ ምር አሸናፊ መ ሆን ችለዋል፡፡
በክብረ እንግድነት የተገኘችው የዓለም የሴቶች ማራቶን ሪከርድ ባለቤቷ ፓውላ ራድክሊፍ ባለፈው አርብ ወደ አዲስ አበባ የገባች ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በመ ምጣቷ ደስተኛ መ ሆኗን ገልፃለች፡፡ የረጅም ዓመ ት የሩጫ መ ድረክ ተፋላሚዋ ደራርቱ ቱሉን “በትራክም ሆነ በጐዳና ላይ የሩጫ ውድድር ሳውቃት ፀባዩዋ አንድ አይነት ነው፡፡ ጥሩ፣መ ልካም እና ለሰው የምታስብ ታላቅ አትሌት ናት፡፡” ስትል ባለፈው አርብ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሒልተን
ሆቴል ጠርቶት በነበረው ጋዜጣዊ መ ግለጫ ላይ ለአውራምባ ታይምስ ገልጻለች፡፡
“መ ሰናበቻ መ ሰናበቻ
የቀረችን ብርቱካን ብቻ
ፍቱልን እሷን ብቻ”
የታላቁ ሩጫ ተሳታፊዎች ከሩጫ ው ጋር በተያያዘ አቤ ቶኪቻው በርካታ ዝርዝር ጉዳዮችን ይዞ በነገው ዕለት ይቀርባል፡፡
(Photo- Awramba Times)
If you don’t see the Amharic fonts , you may click here to read the article in pdf :

























